+251 116 479 500/04 +251 911 516586 info@bigetaplc.com
  • News & Events
  • FAQ
  • Vacancy
  • Facebook
  • YouTube
  • LinkedIn
Bigeta Business PLC.
  • HOME
  • ABOUT BIGETA
    • Mission, Vision & Values
    • Our Team
    • Partners & Stakeholders
    • Our Process
  • SERVICES
    • Construction of Water Supply
    • Construction of Sewerage & Wastewater Treatment
    • Infrastructure
      • Construction of Irrigation & Dam
      • Construction of Road & Bridge
      • Construction of Building
    • Electromechanical Equip Supply & Installation
    • Pipe & Fittings Supply
    • Equipment Import & Rental
    • Real Estate
    • Design Review Services
  • PROJECTS
    • Water Supply Projects
    • Sewerage & Wastewater Treatment Projects
    • Irrigation & Dam Projects
    • Road and Bridge Projects
    • Building Construction Projects
    • Electromechanical Equip Supply & Installation
    • Design Review Project
  • QUALITY
  • HSE POLICY
  • SOCIAL RESPONSIBILITY
  • CONTACT US
Select Page

ከ 4.6 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ በአዳማ እና በባህርዳር ከተማ የፍሳሽ ማጣሪያና ማስወገጃ ግንባታ ውል ስምምነት ተደረገ፡፡

by admin | Nov 15, 2025 | Uncategorized | 1 comment

Source: Ministry of Water and Energy – Ethiopia’s post

14 November at 17:29

ከ 4.6 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ በአዳማ እና በባህርዳር ከተማ የፍሳሽ ማጣሪያና ማስወገጃ ግንባታ ውል ስምምነት ተደረገ፡፡

ጥቅምት 05/2018 ዓ.ም (ው.ኢ.ሚ) የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ከ4.6 ቢሊየን ብር በላይ በሆነ ወጪ በአዳማ እና በባህርዳር ከተማ የፍሳሽ ቆሻሻ ማጣሪያና ማስወገጃ ግንባታ ለማከናወን የውል ስምምነት አደረገ፡፡

ስምምነቱን የፈረሙት የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ሚኒስትር ክቡር ዶ/ር ኢ/ር ሀብታሙ ኢተፋ ፕሮጀክቱ ትልቅ በመሆኑ በቁርጠኝነት ከውሃ አገልግሎት እና ከክልል ውሃ ቢሮዎች ጋር ሀብትን በአግባቡ መጠቀም ላይ ትኩረት በማድረግ እንዲሰሩ አሳስበዋል፡፡

ክቡር ሚኒስትሩ አክለውም ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ አስፈላጊውን ድጋፍና ክትትል እንደሚያደርግ ጠቁመው፤ የአካባቢውን ማህበረሰብ የፕሮጀክቱ ተጠቃሚ ለማድረግ በሚፈለገው ጥራትና በተቀመጠው የጊዜ ገደብ ስራውን አጠናቀው እንዲያስረክቡ አደራ ብለዋል፡፡

የአዳማውን ኮንትራት የፈረሙት የባይጌታ ኮንስትራክሽን ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ተሾመ ታደሰ እና የባህርዳሩን ኮንትራት የፈረሙት የወገሬት ኮንስትራክሽን ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ሚካኤል ወርቁ ሚኒስቴር መ/ቤቱ ለሰጣቸው ዕድል አመስግነው በተያዘለት ጊዜ ገደብና በጥራት ሰርተው እንደሚያስረክቡ ቃል ገብተዋል፡፡

የባህርዳር ከተማ የፍሳሽ ቆሻሻ ማጣሪያና ማስወገጃ ግንባታ ለማከናወን ከወገሬት ኮንስትራከሽን ኃ/የተ/የግ/ኩባንያ ጋር በ2,846,808,381 ብር ወጪ በ18 ወራት የሚጠናቀቅ ውል የተፈረመ ሲሆን ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅ 1,086,534 ህዝብ

ተጠቃሚ በማድረግ በቀን ከ300 እስከ 600 ሺህ ሊትር ፍሳሽ ቆሻሻን የሚያጣራ እንደሆነ ተገልጿል፡፡

በተመሳሳይ የአዳማ ከተማ የፍሳሽ ቆሻሻ ማጣሪያና ማስወገጃ ግንባታ ለማከናወን ከባይጌታ ቢዝነስ ኃ/የተ/የግ/ኩባንያ ጋር በብር 1,804,084,655.89 ወጪ በ18 ወራት የሚጠናቀቅ ሲሆን ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅ 1,040,734 ህዝብ ተጠቃሚ በማድረግ በቀን ከ400 እስከ 950 ሺህ ሊትር ፍሳሽ ቆሻሻን የሚያጣራ እንደሆነ ተገልጿል፡፡

በአዳማ እና በባህርዳር ከተማ የፍሳሽ ቆሻሻ ማጣሪያና ማስወገጃ ግንባታውን ለማከናወን በአጠቃላይ 4,650,893,036.89 ከአለም ባንክ በተገኘ የብድር ድጋፍ የሚከናወን ሲሆን ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅ ለ20 ዓመታት አገልግሎት የሚሰጥ ነው ተብሏል፡፡

HYDROPLAN Ingenieur-HmbH የተባለ የጀርመን ኩባንያ አማካሪ ድርጅት የሁለቱንም ከተሞች የቁጥጥር ስራውን የሚያከናውን በመሆኑ የፍሳሽ ማጣሪያው ከኬሚካል ነፃ በሆነ መንገድ እርስ በርሱ ተብላልቶ በተፈጥሮ መንገድ የሚጣራ በመሆኑ ለማህበረሰቡ ጉዳት በማያመጣ መልኩ ስለሚጣራ የፍሳሹ 70 በመቶ በአግባቡ ተጣርቶ በአቅራቢያው ወደሚገኘው ወንዝ ወይም ወደ እርሻ ይቀላቀላል፤ 30 በመቶው ደረቅ ቆሻሻው ደግሞ ለማዳበሪያነት የሚያገለግል በመሆኑ በተደራጁ ሰው ኃይሎች ለህብረተሰቡ አገልግሎት እንደሚሰጥ ተገልጿል፡፡

ስለተቋማችን ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት

ፌስቡክ

https://www.facebook.com/share/127Jeg3ch6p

ቴሌግራም

http://t.me/mowieethiopia

ዌብሳይት

http://mowe.gov.et

X/ትዊተር

Tweets by mowe_ethiopia

ዩቱዩብ

https://youtube.com/@ministryofwaterandenergy-e8842?s

ቲክቶክ

tiktok.com/@mowetikto

1 Comment

  1. Yonas Muluneh
    Yonas Muluneh on November 19, 2025 at 7:54 am

    Very Well Done

    Reply

Submit a Comment Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Recent Posts

  • Awash Sebat Town Water Supply and Sanitation Project Successfully Completedand Commissioned by BIGETA Business PLC.
  • የከተሞችን የሳኒቴሽን ደረጃ ለማሻሻል የሚያግዝ የአቅም ግንባታ ስልጠና እየተሰጠ ነው።
  • የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ከዓለም ባንክ ጋር በጋራ በ22 ከተሞች ከሚያሰራቸው የፍሳሽ ማጣሪያ ፕሮጀክቶች (Faecal Sludge Treatment Plants) መካከል የአርባምንጭ ከተማ የፍሳሽ ማጣሪያ ፕሮጀክት በጥሩ አፈጻጸም ላይ ከሚገኑት አራት ፕሮጅክቶች መካከል አንዱ መሆኑ ተገለፀ።
  • Christmas Greetings from BIGETA
  • Foundation Stone Laid for Adama Town Faecal Sludge Treatment Plant; BIGETA Business PLC Awarded Construction

Recent Comments

  1. Yonas Muluneh on ከ 4.6 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ በአዳማ እና በባህርዳር ከተማ የፍሳሽ ማጣሪያና ማስወገጃ ግንባታ ውል ስምምነት ተደረገ፡፡
  2. Abraham Yisehak on BIGETA Business PLC. Reinforces Quality Standards with ISO 9001:2015 Refresher Training
  3. Mehidi Hussien on Bigeta Business PLC Signs Contract Agreement with the Ministry of Water and Energyfor the Construction of Dimeka Town Water supply Project

Latest News/Events

Awash Sebat Town Water Supply and Sanitation Project Successfully Completedand Commissioned by BIGETA Business PLC.

Awash Sebat Town Water Supply and Sanitation Project Successfully Completedand Commissioned by BIGETA Business PLC.

Quick Links

  • Construction Solution
  • EM Equipment Supply & Installation
  • Pipe & Fittings Supply & Installation
  • Real Estate Development for Sale & Rent
  • Equipment Supply, Import & Rental

Follow Us

  • FollowFollow
  • FollowFollow
  • FollowFollow
  • FollowFollow
Profile Picture

BIGETA Business P.L.C.

Typically replies within an hour

BIGETA Business P.L.C.

Hey there 👋

How can I help you?

Telegram Start Chat

Contact Us

Lemi Kura Sub- city, CMC Road
Golgota Bldg. Floor 8th,
Addis Ababa, Ethiopia

+251 116 479 500/04

+251 911 516586

info@bigetaplc.com

 www.bigetaplc.com

© 2025 Copyright by Bigeta Business PLC. All rights reserved.

  • CONTACT US
  • Vacancy
  • Privacy Policy